12. ራሱን ሳይሆን እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት የሚሻ መሆኑ
ዳዊት ገና
ሳይቀባ እንኳ የእርሱ ደስታ እግዚአብሔር ደስ ሲሰኝ ማየት ስለሆነ ይህ ደግሞ አምላኩን ደስ አሰኝቶታል፡፡
መዝ.27፡4
“እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት
ዘንድ”
ኤፈ.5፡9-11
“የብርሃኑ ፍሬ በበጎነትና በጽድቅ በእውነትም ሁሉ ነውና ለጌታ ደስ
የሚያሰኘውን እየመረመራችሁ፥ እንደ ብርሃን ልጆች ተመላለሱ፤ፍሬም ከሌለው ከጨለማ ሥራ ጋር አትተባበሩ፥ ይልቁን ግለጡት እንጂ፥”
ሮሜ 12፡2
“የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም
የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።”
1ኛ ጴጥ.2፡5 “እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ
ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን
ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ።”
1ኛ ዮሐ.3፡22 “ትእዛዙንም የምንጠብቅና በፊቱ ደስ የሚያሰኘውን የምናደርግ ስለሆንን የምንለምነውን ሁሉ
ከእርሱ እናገኛለን።”
ዳዊትን ደስ የሚያሰኘው ሁል ጊዜ ኢየሩሳሌምን ማሰብ እና ስለ ኢየሩሳሌም
ማሰብ ወይም ኢየሩሳሌምን አለመርሳት ነው፡፡
መዝ. 137፡5-6 “ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ብረሳሽ፥ ቀኜ ትርሳኝ። ባላስብሽ፥
ምላሴ በጕሮሮዬ ይጣበቅ፤ ከደስታዬ ሁሉ በላይ ኢየሩሳሌምን
ባልወድድ።”
